በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ የተላለፈው ውሳኔ መሻሩን ኦዲትና ኢንስፔክሽን አስታወቀ

(ሳተናው) የሰማያዊ ፓርቲ የስነ ስርዓት ኮሚቴ በቅርቡ ባሳለፈው ውሳኔ የፓርቲውን ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነትን ጨምሮ የስነ ስርዓት ግድፈት ፈጽመዋል ያላቸውን ማባረሩንና ማገዱን መግለጹ አይዘነጋም፡፡

አቶ ይልቃል ጌትነትንና የቀድሞውን የፋይናንስ ኃላፊ ከፓርቲው አባርሪያለሁ ያለው የስነ ስርዓት ኮሚቴው በሌሎች ሁለት የፓርቲው አመራሮች ላይ የሁለት ዓመት እግድ ማስተላለፉ አይዘነጋም፡፡

የስነ ስርዓት ኮሚቴውን ውሳኔ በመመርመር ውሳኔ እንደሚሳልፍ ሲናገር የቆየው የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ በፓርቲው አመራሮች ላይ የተላለፈውን ውሳኔ ህገ ወጥ መሆኑን በመጥቀስ ተባረሩና ታገዱ በተባሉ የፓርቲው አመራሮች ላይ የተላለፈውን ውሳኔ መሻሩን አስታውቋል፡፡

የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ የስነ ስርዓት ኮሚቴውን ውሳኔ የሻረበትን ምክንያት ሲያስረዳም ‹‹ውሳኔው ለተከሳሾቹ ከመድረሱ በፊት በማህበራዊ ድረ ገጾች እንዲሰራጭ በመደረጉ፣የፓርቲውን የመተዳደሪያ ደንብ ያልተከተለና የቅጣትና የስነ ስርዓት ዓላማን ባለማገናዘቡ››ማለቱን በመግለጫው ይነበባል፡፡
የስነ ስርዓት ኮሚቴው ውስጥ የፓርቲው አባላት ያልሆኑ ሁለት ሰዎች ገብተዋል የሚል ወቀሳ በስነ ስርዓት ኮሚቴው ሰብሳቢ ላይ ሲቀርብ ቢቆይም በዚህ ጉዳይ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ ያለው ነገር የለም፡፡

በበማህበራዊ ድረገጾች የፓርቲው አባላት ከዚህ መግለጫ መውጣት ጀምሮ በቃላት መወራረፍን እንዲያቆሙም ኮሚቴው አስጠንቅቋል፡፡
የስነ ስርዓት ኮሚቴው በአመራሮቹ ላይ አሳልፎት የነበረው ቅጣት በመነሳቱም አመራሮቹ በነበራቸው ተሳትፎ እንደሚቀጠሉ ይጠበቃል፡፡

የኦዲትና ኢንስፔክሽን ጠርቶት የነበረው ጠቅላላ ጉባኤ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ለማወቅ የተደረገው ጥረትም አልተሳካም፡፡

Semayawi Letter

Source: Satenaw.com

Add your comment

Your email address will not be published.